“ ልጄ ሆይ እግዚአብሔር ካንተ ጋር ይሁን ስለ አንተም እንደተናገረዉ ያከናዉንልህ
የአምላክህንም የእግዚአብሔርን ቤት ስራ”
መ.ዜና መዋ. ቀዳ. 22፡11
እኛ ካልሆንን ማን ? አሁን ካልሆነ መቼ? ቤተክርስቲያንን ካልሆነ ማንን?
ባሳለፍነዉ አመት በወላይታ ዳዉሮ ሃገረ ስብከት በዱግና ይንጎ ወረዳ የብላቴ አዉደ ፀሐይ ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን
ቤተክርስቲያኑን በቋሚነት ሊረዳ የሚችል የወፍጮ ቤት ፕሮጀክት ነድፎ በሚሰራበት ጊዜ የምንችለዉን የገንዘብ እርዳታ በማድረግ
አሁን አገልግሎት በመስጠት ላይ ይገኛል።
(ተጨማሪ ያንብቡ)
ከ"ፆመ ኢትዮጵያ" ጋር ተያይዞ የመጣልንን፡ ይህን፡ የ"ዓቢይ ፆም" (የሁዳዴ ፆም) ጊዜ፡ ዓቅማችንና የኑሮአችን ኹኔታ በፈቀደልን መጠን፡ በዚያው በጀመርነው፡ በ"ፆመኢትዮጵያ" መንፈስና ሥርዓተ ጸሎት ቀጥለን፡ እናከናውነው ዘንድ፡ ይኸው ቀርቦልናል፤እኛም ኹላችን፡ በነቃና በታጠቀ፡ የኹለንተና አቋም ተቀብለን፡ በአግባቡ ልናስተናግደው እንደተዘጋጀን እናምናለን፡፡
እንደንዑሳን በዓላት ተቈጥረው የሚከበሩ፡ በፆም ወራት የሚውሉ፡ ሰንበታት አሉ፤ እነዚህም፡ "ዓቢይ ፆም"፥ወይም፡ በሕዝባዊ አነጋገር፡ "ሁዳዴ" የሚባለው ፆም፡ ከመግባቱ በፊትና ከገባ በኋላ ያሉት፡ የእሑድ ሰንበታትና ከእነርሱ ጋር የተያያዙት ሳምንታት ናቸው፡፡
ከእነዚህም፡ ቀዳሚዎቹ፡ "መርዓዊ" እና "ዘዘወረደ" የሚል ስያሜ የተሰጣቸው፡ ሰንበታት ናቸው፤"መርዓዊ" የተባለው ሰንበት፡ በቅዱሳት መጻሕፍት ተጽፎ እንደሚነበበው፡ ኢየሱስ ክርስቶስ፡ በዕለተ ዓርብ የሚቀበለው የመስቀል መከራ፡ ለእርሱ፡ የሙሽርነቱ የሠርግ በዓል ስለኾነ፡ ይህች ጽዋውን፡ እንደአርበኛ ወደሚቀበልባት፡ ወደኢየሩሳሌም የጀመረውን ጕዞ የሚያዘክረው ከ"ፆመ ኢትዮጵያ" ጋር ተያይዞ ያለው ዕለተ እሑድ ሲኾን፥የዓቢይ ፆም መግቢያና ለ"ፆመ ሕርቃል" ሰኞ ዋዜማ የኾነው፡ ተከታዩ ዕለተ እሑድ፡ "ዘዘወረደ" ("ቅበላ") የተባለው ነው፡፡ ስለእነዚህና ከዚህ በኋላ ተያይዘው ስለሚቀጥሉት፡ "ቅድስት"፥ "ምኵራብ"፥"መፃጕዕ"፥ደብረ ዘይት"፥"ገብር ኄር" እና "ኒቆዲሞስ" ስለተባሉት፡ የእሑድ ሰንበታት፡ ከዚህ የሚከተሉት አጫጭር መግለጫዎች፡ በመጠኑም ቢኾን ያብራሩላችኋል፡-