ዐቢይ ጾም (የሁዳዴ ጾም)
ፈጣሪያችንና አምላካችን፥ጌታችንና መድሃኒታችን፥ካህን፡ ሊቀ ካህናታችንና ንጉሥ፡ ንጉሠ ነገሥታችን ኢየሱስ ክርስቶስ፡ ለእኛ፡ ለኹላችን ሲል፡ የፆመውን ፆምና የጸለየውን ጸሎት፥ያስተማረውን ትምህርትና ያደረጋቸውን ተአምራት፥የደረሰበትን ፈተናና የታገሣቸውን መከራዎች እያስታወስን፡ (ተጨማሪ ያንብቡ )

ኪነ-ጥበብ
የግብጽ በረሐ ራብ ውኃ ጥሙ፣
የስጋቱ መንገድ መከራ ድካሙ፣
ገና ሳይታሰብ ገና ሳይጀመር፣
የድንግል ማርያም የስደትዋ ነገር፣
በሌሊት ሊናገር የሽሽትዋን ጉዳይ፣
የእግዚአብሔር መልአክ ለዮሴፍ ሳይታይ፣
ከአረጋዊው ስምዖን ድንግል ሰምታ ነበር፣
በነፍስሽ ጦር ያልፋል እያለ ሲናገር።
(ተጨማሪ ያንብቡ )

በገሊላ ቃና በዶኪማስ ቤት
ድንግል አዛኝቱ የአምላክ እናት
እድምተኛው  በዝቶ ወይኑ ሲያልቅባቸው
ጥብብ ጭንቅ ሲሉ ማጠፍያው አጥሯቸው
ወይኑ በማለቁ ዳር ይደርሳል ያለው
ተክዟል ዶኪማስ አለሁልህ በለው
ልጄ ወይኑ አለቀ ብለሽ ስትነግሪው
ጌታም በመታዘዝ ልዩ ወይን ሰጣቸው
ብለሽ እንዳማለድሽ ከእፍረት እንዳዳንሽው
ስለእኔም ባዶነት የኔ ጌታ በይው:: (ተጨማሪ ያንብቡ )

 

የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን የወቅቱ ችግሮች፣ ተግዳሮቶችና ፈተናዎች

በ ዲ.ን ዳንኤል ክብረት
Skip Navigation Links

“ ልጄ ሆይ እግዚአብሔር ካንተ ጋር ይሁን ስለ አንተም እንደተናገረዉ ያከናዉንልህ የአምላክህንም የእግዚአብሔርን ቤት ስራ”

መ.ዜና መዋ. ቀዳ. 22፡11

እኛ ካልሆንን ማን ? አሁን ካልሆነ መቼ? ቤተክርስቲያንን ካልሆነ ማንን?

ባሳለፍነዉ አመት በወላይታ ዳዉሮ ሃገረ ስብከት በዱግና ይንጎ ወረዳ የብላቴ አዉደ ፀሐይ ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን ቤተክርስቲያኑን በቋሚነት ሊረዳ የሚችል የወፍጮ ቤት ፕሮጀክት ነድፎ በሚሰራበት ጊዜ የምንችለዉን የገንዘብ እርዳታ በማድረግ አሁን አገልግሎት በመስጠት ላይ ይገኛል። (ተጨማሪ ያንብቡ)

እንኳን ለብርሃነ ትንሣኤው በሰላም አደረሳችሁ
(www.eotc-nassu.org)

ክርስቶስ ተንሥአ እሙታን፤
       በዐቢይ ኃይል ወሥልጣን፤
አሰሮ ለሰይጣን፤
        
 አግዐዞ ለአዳም፤ 
ሠላም ፤
           እምይዕዜሰ፤
ኮነ፤
          ፍስሐ ወሠላም፡፡
የትንሣኤ መዝሙራት
Skip Navigation Links
 

"ዓቢይ ፆም" - "የሁዳዴ ፆም"

ፈጣሪያችንና አምላካችን፥ጌታችንና መድኃመሄታችን፥ካህን፡ ሊቀ ካህናታችንና ንጉሥ፡ ንጉሠ ነገሥታችን ኢየሱስ ክርስቶስ፡ ለእኛ፡ ለኹላችን ሲል፡ የፆመውን ፆምና የጸለየውን ጸሎት፥ያስተማረውን ትምህርትና ደረጋቸውን ተአምራት፥የደረሰበትን ፈተናና የታገሣቸውን መከራዎች እያስታወስን፡ እኛ ኹላችን፡ የእርሱን ፈለግ ተከትለን፡እነዚህን የሃይማኖት ምግባራት፡ በእየራሳችን ፈቅደን፡ በነፍስ፥በሥጋና በመንፈስ እየፈጸምንየምንሳተፍበትን፡ የዘንድሮውን "ዓቢይ ፆም" - "የሁዳዴ ፆም" የምንለውን፡ ታላቁ ፆማችንን፡እነሆ፡ በያለንበት ለመቀበል ስላበቃን፡ ልዑል እግዚአብሔርን እናመሰግነዋለን፡፡
+ + +

በቅዱሱ ኪዳን፡ የእግዚአብሔር መንግሥትና ድንግል ማርያም የኾነችው፡


የኢትዮጵያ ልጆች!
በአገር ላላችሁትና በመላው ዓለም ለተበተናችሁት!
የተለመደው ኢትዮጵያዊ ሰላምታችን ይድረሳችሁ!

ከ"ፆመ ኢትዮጵያ" ጋር ተያይዞ የመጣልንን፡ ይህን፡ የ"ዓቢይ ፆም" (የሁዳዴ ፆም) ጊዜ፡ ዓቅማችንና የኑሮአችን ኹኔታ በፈቀደልን መጠን፡ በዚያው በጀመርነው፡ በ"ፆመኢትዮጵያ" መንፈስና ሥርዓተ ጸሎት ቀጥለን፡ እናከናውነው ዘንድ፡ ይኸው ቀርቦልናል፤እኛም ኹላችን፡ በነቃና በታጠቀ፡ የኹለንተና አቋም ተቀብለን፡ በአግባቡ ልናስተናግደው እንደተዘጋጀን እናምናለን፡፡

የዓቢይ ፆም ሰንበታትና ሰሙናት፡፡

እንደንዑሳን በዓላት ተቈጥረው የሚከበሩ፡ በፆም ወራት የሚውሉ፡ ሰንበታት አሉ፤ እነዚህም፡ "ዓቢይ ፆም"፥ወይም፡ በሕዝባዊ አነጋገር፡ "ሁዳዴ" የሚባለው ፆም፡ ከመግባቱ በፊትና ከገባ በኋላ ያሉት፡ የእሑድ ሰንበታትና ከእነርሱ ጋር የተያያዙት ሳምንታት ናቸው፡፡ ከእነዚህም፡ ቀዳሚዎቹ፡ "መርዓዊ" እና "ዘዘወረደ" የሚል ስያሜ የተሰጣቸው፡ ሰንበታት ናቸው፤"መርዓዊ" የተባለው ሰንበት፡ በቅዱሳት መጻሕፍት ተጽፎ እንደሚነበበው፡ ኢየሱስ ክርስቶስ፡ በዕለተ ዓርብ የሚቀበለው የመስቀል መከራ፡ ለእርሱ፡ የሙሽርነቱ የሠርግ በዓል ስለኾነ፡ ይህች ጽዋውን፡ እንደአርበኛ ወደሚቀበልባት፡ ወደኢየሩሳሌም የጀመረውን ጕዞ የሚያዘክረው ከ"ፆመ ኢትዮጵያ" ጋር ተያይዞ ያለው ዕለተ እሑድ ሲኾን፥የዓቢይ ፆም መግቢያና ለ"ፆመ ሕርቃል" ሰኞ ዋዜማ የኾነው፡ ተከታዩ ዕለተ እሑድ፡ "ዘዘወረደ" ("ቅበላ") የተባለው ነው፡፡ ስለእነዚህና ከዚህ በኋላ ተያይዘው ስለሚቀጥሉት፡ "ቅድስት"፥ "ምኵራብ"፥"መፃጕዕ"፥ደብረ ዘይት"፥"ገብር ኄር" እና "ኒቆዲሞስ" ስለተባሉት፡ የእሑድ ሰንበታት፡ ከዚህ የሚከተሉት አጫጭር መግለጫዎች፡ በመጠኑም ቢኾን ያብራሩላችኋል፡-

 የአንድነት ጉባኤው መተዳደሪያ ደንብ
Skip Navigation Links

 

የ፲ኛው ጠቅላላ ጉባኤ ፎቶ
የ፲ኛው ጠቅላላ ጉባኤ ፎቶ



የምሥራቅ ዞን አንድነት ጉባኤ ዘገባ

ለተጨማሪ መረጃ
ሌሎች ድረ-ገጾች

የምስራቅ ዞን የ2004 ዓ ም የመጀመርያ ዙር ጉባኤውን በዋሽንግተን ዲሲ አካሔደ

በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ አሜን

የምስራቅ ዞን የ2004 ዓ ም የመጀመርያ ዙር ጉባኤውን በዋሽንግተን ዲሲ አካሔደ

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን በሰሜን አሜሪካ የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ጉባኤ የምስራቅ ዞን የ2004 ዓ ም የመጀመርያ ዙር ጉባኤውን መምህራነ ወንጌል፣ ዘማርያን፣ እንዲሁም ከየእስቴቱ የመጡ ወጣት የሰንበት ትምህርት ቤት ተማሪዎች በተገኙበት በዋሽንግተን ዲሲ ግዛት ኖርዝ ዌስት ዲሲ በታላቅ ድምቀት ተከብሮ ዋለ።

ከቀኑ ፯ ተኩል ከ፸ በላይ የሚሆኑ የሰንበት ትምህርት ቤት ዓባላት የተገኙበት መርሃግብር በጸሎት ተከፍቶ እንደተጀመረ የምስራቅ ዞን አጠቃላይ የስራ ሂደት እና አተገባበር {REPORT} በሂሳብ ክፍሉዋ ኃላፊአማካኝነት የቀረበ ሲሆን ከተሰብሳቢዎች የተነሱ ጥያቄዎችን በስራ አመራር ላይ ያሉ ወንድሞች መልሰዋል።

በእለቱ የተገኙት መምህር ዲያቆን ኤፍሬም እሸቴ ስለ አንዲት ቅድስት ቤተክርስቲያን ምንነት በሰፊው ካስተማሩ በኋላ ስለወቅታዊው የቤተክርስቲያን ፈተና በተለይም እንደሰደድ እሳት እየተፋፋመ ያለውን የተሃድሶ እንቅስቃሴ እና ስለ ወቅታዊው የሰሜን አሜሪካ ቀኖና ቤተክርስቲያን መጣስ አስመልክቶ በሰፊው አወያይተዋል። Skip Navigation Links

ያለፉ ጽሁፎች..፩  |  |  |  |