ከዴንቨር ደብረ ሰላም መድኃኔዓለም
ቤተክርስቲያን የፈለገ ህይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ጋር የተደረገ ቃለ ምልልስ
የዴንቨር መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን የተመሰረተው ሚያዝያ ፪ ቀን ፲፱፱፯ ዓ. ም ሲሆን፤ ለቤተክርስቲያኒቱ መመስረት
ምክንያት የሆነውም በ ፲፱፺ ዎቹ በአብዛኛው በሰሜን አሜሪካ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ተፋፍሞ የነበረው
የመለያት ችግር ሲሆን በዚሁ በዴንቨርም ቤተከርስቲያን የዘረኝነትና የፖለቲካ ዓላማ ማካሄጃ እንዳትሆን ይጋደሉ የነበሩ እውነተኛ
ምዕመናን በደረሰባቸው ችግር ምክንያት ነው፡፡ እነዚሁ ምዕመናን ከቤተክርስቲያኒቱ በፓሊስ ኃይል ተገደው እስኪወጡ ድረስ
በመገፋታቸው በእምነታቸው በመጽናት ተጋድሎዋቸውን በመቀጠል በወቅቱ የአገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ በነበረት በነበሩት በአቡነ ማትያስ
መልካም ፈቃድና በእግዚአብሔር ቸርነት ቤተክርስቲያኒቱ ልትቋቋም ችላለች፡፡ ሰንበት ት/ቤቱም ይህንን ተከትሎ በግንቦት ፪ ቀን
፲፱፺፯ዓ ም ተቋቊሟል ፡፡ ሰንበት ት/ቤቱም በ ፳፻ ዓ. ም ፈለገ ህይወት የሚለውን መጠሪያ በአባቶች ተሰይሞለታል የፈለገ
ህይወት ሰንበት ት/ ቤት በአሁኑ ወቅት ፴፭ የሚሆኑ አባላት አሉት፡፡ (
ተጨማሪ ያንብቡ
)