በመልአኩ በቅዱስ ገብርኤል አብሳሪነት አምላካችን ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም ከሥጋዋ ሥጋ ከነፍስዋ ነፍስ ነስቶ ወደዚህ ዓለም በመምጣት አምላካዊ ትእዛዝን ተላልፎ ካልተፈቀደለት ገበታ የተመገበውን እና በዚህም ምክንያት ከገነት የተሰደደውን አዳምን ወደ ቀደመ ክብሩ ለመመለስ ከተወለደበት ከሕፃንነቱ ጀምሮ ታላቅ የሆነ መከራ እና እንግልት ደርሶበታል፤ ሕማምን እና ስደትን ተቀብሏል። እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምም የበኲር ልጅዋን ጌታችንን በወለደች በአርባኛው ቀኗ እንደ ኦሪቱ ሕግ መሥዋዕት ለማቅረብ ወደ ኢየሩሳሌም በሔደችበት ጊዜ አስቀድሞ ትንቢት የተነገረለትና በጌታም የተቀባውን ሳያይ ሞትን እንዳያይ በመንፈስ ቅዱስ ተረድቶ የነበረው አረጋዊው ስምዖን ጌታን ታቅፎ "እነሆ፥ የብዙዎች ልብ አሳብ ይገለጥ ዘንድ፥ ይህ በእስራኤል ላሉት ለብዙዎቹ ለመውደቃቸውና ለመነሣታቸው ለሚቃወሙትም ምልክት ተሾሞአል፥ በአንቺም ደግሞ በነፍስሽ ሰይፍ ያልፋል።" ሉቃ.፪፡፴፬-፴፭ በማለት እንደተናገረው ቃል ሔሮድስ ሰማያዊውን ንጉሥ ኢየሱስ ክርስቶስን የምድራዊ ንጉሥ አድርጎ በማሰብ እና ሥልጣኔን ይወስድብኛል ብሎ በመፍራት እድሜአቸው ሁለት ዓመት እና ከዚያ በታች የሆኑትን ሕፃናት ለማስገደል ትእዛዝ አስተላለፈ፤ ትእዛዙም ተግባራዊ ሆነ። (ተጨማሪ ያንብቡ )
ከመቶ ዓመታት በፊት የግብጽ ቤተ ከርስቲያን በአራት ነገሮች ትቀስፋ ትንገላታ ንበር፡፤የእንግሊዝን ቅኝ ግዝት ትክትሎ ብመጣው የፕሮቴስትንት ወረራ የእስልም ወንድማማቾች በሚያቀነቅኑት አክራሪ እስልምና ዓላማቸውን የዘነጉ ጳጳሳትና ክህናት ከወቅቱ መንግሥት ጋር ገጥመው (ተጨማሪ ያንብቡ )