መጀመሪያ ቀን ሪፖርት

መጀመሪያ ቀን ፎቶዎች

፲፩ኛ ዓመታዊ ጉባኤ በዴንቨር ኮሎራዶ ደብረ ሰላም መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን ነሐሴ ፳፱, ፳፻፫ ዓ.ም (Sep. 02, 2011)

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ የሰ/ት/ቤቶች አንድነት ፲፩ኛ ዓመታዊ ጉባኤ በዴንቨር ኮሎራዶ ደብረ ሰላም መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን ነሐሴ ፳፱, ፳፻፫ ዓ.ም (Sep. 02, 2011) ብፁዕ አቡነ ኤዎስጣጤዎስ የሰሜን ምእራብ አሜሪካ ካሊፎርኒያ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ አብርሃም የዋሽንግተን ዲሲ እና አካባቢዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ካህናት ተጋባዥ መምህራን እንዲሁም ከተለያዩ የአሜሪካ ግዛቶች የመጡ የጉባኤው ተሳታፊዎች በተገኙበት ጉባኤው ከምሽቱ 12:00 (6:00 PM) በጸሎት ተጀመረ በማስከተልም የፈለገ ህይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ተወካይ የእንኳን ደህና መጣችሁ መልእክት አስተላልፈዋል የሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ኤዎስጣጤዎስም <<አስተጋብኦሙ ለሀውርት እምጽባህ"="">> ከሚለው ከቅዱስ ያሬድ ድርሰት በተወሰደ ኃይል ቃል መሰረት ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ከወጣቱ ትውልድ የምትጠብቀውን መጠነ ሰፊ አገልግሎት በዝርዝር አውስተው በተጨማሪም የጉባኤው ተሳታፊዎች በመጪው ቀናት የሚካሄዱትን መርሃ ግብሮች በንቃት እንዲሳተፉ በማሳሰብ የእለቱን ትምህርታቸውን አጠናቀዎል:: በማጠቃለያም የሰ/ት/አ/ጉባኤ ዋና ሰብሳቢ የሆኑት ዲ/ን ብዙአየሁ ልመንህ በቀጣዮቹ ቀናት የሚካሄዱትን መርሃ ግብሮች በዝርዝር በመግለፅ እና ጉባኤውን ለመሳተፍ ለመጡት ተሳታፊዎች የሚጠበቅባቸውን የተሳታፊነት ድርሻ የሚገልጽ መልእክት አስተላልፈዋል:: በማጠቃለያም የእራት መስተንግዶ ከተደረገ በኃላ የእለቱ መርሃ ግብር ከምሽቱ 3:00 (9:00 PM ) ተፈፅሟል::

ሁለተኛ ቀን ቀን ሪፖርት

ሁለተኛ ቀን ፎቶዎች

በኢ/ኦ/ተ/ ቤተ ክርስቲያን የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ጉባዔ የሁለተኛ ቀን መርሃ ግብር ከጠዋቱ 3፡00 (9፡30 PM) በብጹዓን አባቶች ፀሎት ተጀመረ። በማስከተልም በአዘጋጁ ሰ/ት/ቤት ሰብሳቢ በሙሉጌታ ነጋሽ “የአንድ አካል ብልት ነን” በሚል ርዕስ ስነ ግጥም ቀርቧል። በመቀጠልም የዋሽንግተን ዲሲና አካባቢ ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ አብርሃም ከመጽሐፈ ኢያሱ ም. ፳፫፥፮ “በሙሴ ህግ የተፃፈውን ለመፈጸም ትጉ....” የሚለውን ሃይለ ቃል መሰረት በማድረግ ወጣቱ ትውልድ የቀደሙትን አባቶች ፈለግ መከተል፤ የአበውን ህግ በማክበር እና በማስከበር፤ ህገ ቤተክርስቲያንን በመጠበቅና በማስጠበቅ ደረጃ ሊወጣው የሚገባውን ሃላፊነት በዝርዝር በመግለፅ ሰፋ ያለ ትምህርት ሰጥተዋል። የብፁዕነታቸውን ትምህርት በማስከተልም ዲ/ን ዳንኤል ክብረት “የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን የወቅቱ ችግሮች ተግዳሮቶች እና ፈተናዎች” በሚል ርዕስ ሰፊ ጥናታዊ ፅሁፍ ያቀረበ ሲሆን ይህንን ጥናታዊ ፅሁፍ መሰረት በማድረግ የጉባኤው ታዳሚዎች ጥያቄዎችና አስተያየቶቻቸውን ያቀረቡ ሲሆን ለጥያቄዎቹም መልስና ማብራሪያ በብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳትና በፅሁፉ አዘጋጅ በዲ/ን ዳንኤል መልስ ተሰጥቶበታል። የጠዋቱ መርሐ ግብር ከመጠናቀቁ በፊት ከሳንሆዜ እና ከኦክላንድ አብያተክርስቲያናት የመጡ የሰንበት ት/ቤት አባላት ‘’የቃዴስ ምድር” በሚል ርዕስ መነባንብ አቅርበዋል። በዚሁ 11ኛው ዓመታዊ ጉባዔ ላይ ከ14ት የአሜሪካ ግዛቶች ውስጥ የሚገኙ 25ት ሰንበት ት/ቤቶች የተውጣጡ ቁጥራቸው ከ200 የማያንሱ አባላት ተገኝተዋል።ይህ የተሳታፊዎች ቁጥር በየሰዓቱ እየጨመረ ይገኛል።ከቀኑ በ2፡00 ሰዓት የጠዋቱ መርሐ ግብር ተጠናቋል።

በሁለቱም ቀናት የነበሩ ቪዲዮዎች በከፊል