‹‹የመስቀሉ ቃል ለሚጠፉት ሞኝነት ለኛ ለምንድን ግን የእግዚአብሔር ኃይል ነውና››1ኛ ቆሮ 1፡18
የመስቀል ደመራ በዓል በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ሃይማኖት ተከታዮች ዘንድ በመላው ኢትዮጵያ እንዲሁም ኦርቶዶክስ ኢትዮጵያዉያን በሚኖሩበት ሁሉ በታላቅ ድምቀት በየአመቱ መስከረም 16 እና 17 ይከበራል፡፡ወፍ እንደ ሃገሯ ትጩሃለች እንዲሉ በምንኖርበት በሰሜን አሜሪካም ከጥቂት አብያተክርስቲያናት በስተቀር የኑሮዉ ሁኔታ እንደፈቀደ ብዙዉን ጊዜ ቅዳሜ እና እሁድን ተገን አድርገን መስቀልን ጨምሮ ሌሎችንም በዓላት እናከብራለን፡፡ ተጨማሪ ያንብቡ  
ጉባኤውን በተመለከተ የተዘጋጀውን ገጽ ይጎብኙ

የሁለቱንም ቀን ጉባኤ በተመለከት የተዘጋጀውን ሪፖርት፣ ፎቶና ቪዲዮዎች ይህንን ሊንክ በመጫን ይመልከቱ(ተጨማሪ ያንብቡ )

Skip Navigation Links
Skip Navigation Links
Skip Navigation Links
 የአንድነት ጉባኤው መተዳደሪያ ደንብ
Skip Navigation Links
Skip Navigation Links

“ሞተ በፈቃዱ ወተቀብረ በሥምረቱ” ሃይማኖተ አበው ዘአትና. እንዲል። በፈቃዱ ሞቶ በውዱ ተቀብሮ ሦስት ቀን ሦስት ሌሊት በከርሠ መቃብር አድሮ መግነዝ ፍቱልኝ መቃብር ክፈቱልኝ ሳይል በገዛ ሥልጣኑ በዘመነ ማርቆሰ እሑድ በመንፈቀ ሌሊት ተነስቷል። “ወተንሣእኩ በሥልጣነ - ባሕቲትየ” እንዳለ ቅዱስ ቄርሎስ።ተጨማሪ ያንብቡ
 ፲፩ኛ ዓመታዊ ጉባኤ ከነሐሴ ፳-፳፻፫ - ከነሐሴ ፳፱-፳፻፫ ዓ.ም /Sep2 2011- Sep4 2011/

በመርሐ ግብሩ መክፈቻ ዓርብ ነሐሴ ፳፱ ብጹዕ አቡነ ኤዎስጣጤዎስ የሰሜን ምዕራብ አሜሪካ ካሊፎርንያ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፤ ብጹዕ አቡነ አብርሃም የዋሽንግተን ዲሲ እና አካባቢዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፤ ካህናትና ተጋባዥ መምህራን እንዲሁም ከ፲ የአሜሪካ ግዛቶች ከ ፳፪ ሰ/ት/ቤቶች የመጡ ፻፴-፻፶ የሰ/ት/ቤት አባላት በመርሐ ግብሩ የመክፈቻ ዕለት ተገኝተዋል፡፡በዕለቱም ብጹዕ አቡነ ኤዎስጣቴዎስ አጠር ያለ ትምህርት በማጠቃለያም የሰ/ት/ ቤቶች አንድነት ጉባኤ ዋና ሰብሳቢ የሆኑት ዲ/ን ብዙአየሁ ልመንህ በቀጣዮቹ ቀናት የሚካሄዱትን መርሃ ግብሮች በዝርዝር በመግለፅ እና ጉባኤውን ለመሳተፍ የመጡት ተሳታፊዎች የሚጠበቅባቸውን የተሳታፊነት ድርሻ የሚገልጽ መልእክት አስተላልፈዋል:: በማጠቃለያም የእራት መስተንግዶ ከተደረገ በኃላ የዕለተ አርብ ጉባኤ ፍጻሜ ሆናል፡፡

የቅዳሜው መርሐ ግብር ከጠዋቱ 3.30/ 9.30 a.m/ ተጀምሯል፡፡በዚህ ቀን በመርሐ ግብሩ ላይ የተገኙ አባላት ቁጥር ጨምሮ ከ፲፬ ክፍለ ግዛቶች/ States/ ከ ፳፭ ሰንበት ትምህርት ቤቶች ቁጥራቸው ወደ ፪፻ የሚደርስ የሰንበት ት/ቤት አባላት ተገኝተዋል፡፡ በቅዳሜው ጠዋት መርሐ ግበር ላይ ሰፊውን ሰዓት ይዞ የነበረው በ ዲ.ዳንኤል ክብረት ‘’የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን የወቅቱ ችግሮች ተግዳሮቶች እና ፈተናዎች’’ በሚል ርዕስ የቀረበው ሰፊና ጥልቅ የሆነው ጥናታዊ ጽሁፍ ሲሆን በቀረበው ጽሁፍ ላይም የቤተክርስቲያንን ችግሮችና ፈተናዎችን በሰፊው አሳይቷል፡፡ በቀረበው ጽሁፍ ላይም የብጹአን አባቶች አስተያየትና የተሳታፊዎች ጥያቄና አስተያየት ቀርቦበታል፡፡

በቅዳሜው የከሰዓት በኃላ መርሐ ግብር ሰፊውን ሰአት ከያዙት መርሐ ግብሮች አንዱ የነበረው በቀሲስ ዶ/ር መስፍን ተገኝ “በሰሜን አሜሪካ የኢ/ኦ/ተ/ቤተክርስቲያን አህጉረ ስብከትን ለማጠናከር ትኩረት የሚሹ ጉዳዮችና የሰንበት ት/ቤቶች ድርሻ” በሚል ርዕስ የቀረበው ጥናታዊ ፅሁፍ ሲሆን በጽሁፉ ላይም አህጉረ ስብከቶች ያለባቸውን ችግርና የመፍትሔ ሐሳቦችን የጠቆመ ነበር፡፡በየመርሐ ግብሩ መካከል ከተለያዩ ሰ/ት/ቤቶች የመጡ አባላት በተናጥልና በህብረት በመሆን የተለያዩ ያሬዳዊ ዝማሬዎች እና መንፈሳዊ ግጥሞች አቅርበዋል፡፡ ይህ ደግሞ ጉባኤውን አስተማሪና የተለያዩ ሰ/ት/ቤቶች ልምድ የሚለዋወጡበት እና የተሻለ አገልግሎት ለማቅረብ የሚተጉበት እንዲሆን አድርጎታል፡፡  በዚሁ የቅዳሜው መርሐ ግብር ላይ የአብዛኛው አባላትን ትኩረት የሳበውና የራሱን መንፈሳዊ ህይወት እንዲዳስስ ያደረገው መርሐ ግብር ደግሞ በ፲፪ ዓመቱ ወደ አሜሪካን አገር ከቤተሰብ ጋር የመጣውና የተቀበለውን የማዕረገ ዲቁና ትምህርት ይበልጥ ለማስፋፋት የአስራ ሁለተኛ ክፍል ትምህርቱን እንዳጠናቀቀ ለ ፫ ዓመታት ወደ ኢትዮጵያ ገዳማት ለመንፈሳዊ ትምህርት በሄደው በዲ. ኤፍሬም ስለሺ ህይወት ዙሪያ የተደረገው ቃለ መጠይቅ ነበር ፡፡

እሁድ ጠዋት ጉባኤውን ለመባረክ እና ለመምራት በመጡት ሊቃነ ጳጳሳት ስርዓተ ቅዳሴ በሁለቱም አብያተ ክርስቲያናት(በደብረ ሰላም መድኃኔዓለም እና በደብረ ገነት ኪዳነ ምህረት)ተከናውኗል፡፡ የከሰዓት በኃላውን ሰፊውን ሰዓት ይዞ የነበረው መርሐ ግብር ደግሞ የአንድነት ጉባኤው የአራት አመት ስልታዊ ዕቅድ/strategic plan/ ሲሆን ይህ ስልታዊ ዕቅድ የአንድነት ጉባኤው በቀጣዮቹ አራት ዓመታት እንደ እግዚአብሔር ቅዱስ ፈቃድ ሊያከናውናቸው ይገባል ያላቸውን ነጥቦች አስቀምጧል፡፡ በዚህ ርዕስ ዙሪያም አባላትን በአምስት ምድብ በመከፋፈል ሰፊ ውይይት ከተደረገበት በኃላ የተሰጡት ሃሳቦች በአንድነት ተጠቃለው ለስራ አመራሩ ተሰጥቷል፡፡

የእሁድ ዕለት የማጠቃለያ መርሐ ግብር የነበረው የአንድነት ጉባዔውን የገንዘብ አቅም ለማጠናከር የተደረገው ውይይት ሲሆን በዚህ ውይይት አብዛኛው አባላት ለአንድነት ጉባኤው ያለውን የእኔነት ስሜት ያሳየበት ነበር፡፡በዚሁ መርሐ ግብር ላይም የጉባዔውን የገንዘብ አቅም ለማጠናከር በተደረገው ልዩ የገንዘብ ማሰባሰቢያ መርሀ ግብር አማካይነት ከጉባኤው ተሳታፊዎች እና ጉባኤውን በመገናኛ ብዙሃን ከሚከታተሉ ወንድሞች እና እህቶች አስር ሺህ/፼/ ዶላር እና ለሊቃነ ጳጳሳት ሶስት የአውሮፕላን ቲኬት ወጪ ለማሰባስብ ተችሏል፡፡ በአጠቃላይ የዘንድሮው ፲፩ኛ ዓመት ጉባኤ የተሳካና የሰ/ት/ቤት አባላቱ የአንድነት ጉባኤውን ለማጠናከር፤ ከአባቶች ጋር አብሮ በመስራት አህገረ ስብከትን ለማጠናከር ተነሳሽነታቸውን ያሳዩበት ነበር፡፡

ወስብሐት ለእግዚአብሔር

የስቅለትና የትንሳኤ ግጥሞች
Skip Navigation Links


ሰሙነ ህማማት
ከአባታችን አዲም በዯሌ ወይንም ስሕተት በኋሊ በሕማማት፣ በዯዌያት፣ በመቅሰፍታት፣ ወዘተ በብዙ መከራ የሰው ሌጅ ሉኖርባቸው ግዴ የሆነባቸው ዘመናት ጥቂቶች አሌነበሩም፡፡ ጥሮ ግሮ ወጥቶ ወርድ ሇፍቶ ማስኖ የዕሇት ጉርስ የቀን ሌብስ ማግኘት እጅግ አዲጋች ነበር፡፡ ተጨማሪ ያንብቡ
ዐቢይ ጾም (የሁዳዴ ጾም)
ፈጣሪያችንና አምላካችን፥ጌታችንና መድሃኒታችን፥ካህን፡ ሊቀ ካህናታችንና ንጉሥ፡ ንጉሠ ነገሥታችን ኢየሱስ ክርስቶስ፡ ለእኛ፡ ለኹላችን ሲል፡ የፆመውን ፆምና የጸለየውን ጸሎት፥ያስተማረውን ትምህርትና ያደረጋቸውን ተአምራት፥የደረሰበትን ፈተናና የታገሣቸውን መከራዎች እያስታወስን፡ (ተጨማሪ ያንብቡ )

 
ቤተልሔም እንሂድ ሉቃ ፪፥፲፭
የ፲ኛው ጠቅላላ ጉባኤ ፎቶ
ኪነ-ጥበብ
የግብጽ በረሐ ራብ ውኃ ጥሙ፣
የስጋቱ መንገድ መከራ ድካሙ፣
ገና ሳይታሰብ ገና ሳይጀመር፣
የድንግል ማርያም የስደትዋ ነገር፣
በሌሊት ሊናገር የሽሽትዋን ጉዳይ፣
የእግዚአብሔር መልአክ ለዮሴፍ ሳይታይ፣
ከአረጋዊው ስምዖን ድንግል ሰምታ ነበር፣
በነፍስሽ ጦር ያልፋል እያለ ሲናገር።
(ተጨማሪ ያንብቡ )

በገሊላ ቃና በዶኪማስ ቤት
ድንግል አዛኝቱ የአምላክ እናት
እድምተኛው  በዝቶ ወይኑ ሲያልቅባቸው
ጥብብ ጭንቅ ሲሉ ማጠፍያው አጥሯቸው
ወይኑ በማለቁ ዳር ይደርሳል ያለው
ተክዟል ዶኪማስ አለሁልህ በለው
ልጄ ወይኑ አለቀ ብለሽ ስትነግሪው
ጌታም በመታዘዝ ልዩ ወይን ሰጣቸው
ብለሽ እንዳማለድሽ ከእፍረት እንዳዳንሽው
ስለእኔም ባዶነት የኔ ጌታ በይው:: (ተጨማሪ ያንብቡ )

   
ጠቃሚ ድረ-ገጾች
Skip Navigation Links
  ያለፉ ጽሁፎች..፩  |